Page 149 - አብን
P. 149

አብን




                  የኢትዮጵያ  የውኃ  ኃብት  ልማት  ፓሊሲ  መሰረታዊ
                    ችግሩ የቆየውን  ነባራዊ  ሁኔታ የማስጠበቅ  አዝማሚያ
                    ያለው መሆኑ ነው፡፡ ይህም በውኃ ኃብት ልማት ዘርፉ
                    መንግስት        ዋነኛ      ኢንቬስተር፣የውኃ           ፕሮጀክቶች
                    ተግባሪና  አስተዳዳሪ  ሆኖ  መቀጠሉ  ነው፡፡  የመንግስት
                    ድርሻ  በዚህ  ደረጃ  ከፍተኛ  በሆነበት  ሁኔታ  የውኃ
                    አቅርቦት ችግሩን መቅረፍ አይችልም፡፡ ስለዚህ የአማራ
                    ብሔራዊ  ንቅናቄ(አብን)  የውኃ  ኃብት  ልማት  ፓሊሲ

                    መንግስት  በውኃ  ልማት  ዘርፉ  ያለውን  የገዘፈ  ሚና
                    እንዲቀንስ  በማድረግ  የግሉ  ዘርፍ  እንዲሳተፍበት
                    ያደርጋል፡፡  መንግስት  ሁሉንም  የውኃ  አገልግሎት
                    ከመስጠት        ወጥቶ       ወደ      ማስተባበር፣        አቅጣጫ
                    ማስያዣና  የሕግና  ቁጥጥር  ሥርዓት  ወደ  መምራት
                    እንዲያተኩር ይደረጋል፡፡

                  የውኃ  ኃብት  እንክብካቤያችንና  የልማት  አቀራረባችን
                    ከፍተኛ  የሆነ  የቅንጅት  ችግር  አለባቸው፡፡ስለዚህ
                    የሚተገበሩ  የውኃ  ልማት  ፕሮጅክቶች  በተቀናጀ
                    መንገድ እንዲተገበሩ ያደርጋል፡፡የመጠጥ ውኃ፣ የፍሳሽ
                    ማስወገድ፣ ጤናና ንጽህና ሥራዎች በተቀናጀ መሰረት
                    የሚተገበር መሆን አለበት፡፡

                  የውኃ  ኃብት  ልማት  ሥራዎች  የተለያዩ  ዘርፎችን

                    ፍላጎት      (sectoral     demand)      መሰረት       ያደረገ
                    (የመኖሪያ  ቤቶች፣  የኢንዱስትሪ፣  የእርሻው  ዘርፍና
                    የተፈጥሮ  ፍሰት  ፍላጎቱን  (environmental  flow


             147    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   144   145   146   147   148   149   150   151   152   153   154