Page 14 - Descipleship 101
P. 14
የእምነት ውጤቶች
በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ ከእምነት የተነሳ ስለተፈጸሙት ሁለት ነገሮች እስኪ እንመልከት፡
1. ከእምነት የተነሳ እግዚአብሄር ደስ ይለዋል (ዕብ.11፡5-6)።
2. ከእምነት የተነሳ ሰው በክርስቶስ ሲያምን ይድናል፤ ይጸድቅማል (ሮሜ. 5፡1፤ ኤፌ.2፡8-9፤ ሐዋ.26፡18)።
ከታች የተዘረዘሩትን ጥቅሶች አንብብና እራስህን ጠይቅ፤ ማን እምነት ነበረው ሴቲቱ ወይስ ልጁ?
ማቴ.15፡28___________________________________________________
“በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ፡- አንቺ ሴት እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰአት ጀምሮ ዳነች።”
ማር.5፡34___________________________________________________
“እርሱም፡- ልጄ ሆይ እምነትሽ እድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ ከስቃይሽም ተፈወሽ አላት”
ሉቃ.7፡50___________________________________________________ ሴቲቱንም፡- እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ አላት።
13