Page 66 - DINQ MAGAZINE OCTOBER 2020 EDITION
P. 66

World
                                                                                                      Africa





         በኮቪድ 19 ምክንያት መኖሪያ  ቤት ያጡት ግለሰብ  አቶ ማርቆስ ኮኩትስ እስከ
         ህይወታቸው መጨረሻ ድረስ መኖሪያ ቤት አገኙ


         ማህበረ  ረድኤት  የተሰኘ  ግብረ  ሰናይ  ድርጅት  እና  አቶ  ማርቆስን  ከጎዳና
         ለመታደግ ተባብረው ሲሰሩ የነበሩት ጥምር ኮሚቴ ስራቸውን አጠናቀው ቤቱን
         ለአቶ ማርቆስ ገንዘቡን ለሞግዚት አስረከቡ።

         ነገሩ እንዲህ ነው ፣ ከ35 ዓመት በላይ አትላንታ ውስጥ የኖሩት አቶ ማርቆስ
         በአደረባቸው  የአእምሮ  መረበሽ  የተነሳ  እና  በኮቪድ  ወረርሽኝ  ምክንያት  ቤት
         የሚያከራያቸው  ባለመገኘቱ  የተነሳ  ጎዳና  ላይ  መውደቃቸውን  የተመለከቱ
         ኢትዮጽያውያን እና ኤርትራውያን ለማህበረ ረድኤት በመንገር እና በአካባቢው
                                                                                    09/30/2020
         ያሉትን አበሾች በማስተባበር በጋራ ስራ ከጀመሩ ከሁለት ወር በሁዋላ ስራቸውን                         Johns Hopkins University    Africa CDC Dashboard
         አጠናቀዋል። ምንም እንኳን ማህበረ ረድኤት እና አስተባባሪ ኮሚቴው ለግለሰቡ
         መኖሪያ ቤት ለመግዛት አስበው ስራቸውን  ቢጀምሩም ዉጤቱ እነርሱም  ሆኑ                                                 Georgia
         አትላንታ  አካቢው  ያሉት  አበሾች  ያልጠብቁት  ሆኖ  ሁሉንም  ተዐምር
         አስብሉአል።

         ማህበረ  ረድኤት  እና  ኮሚቴው    በከፈቱት  የጎፈንድሚ  አካዉንት
         ከ$54000.00  በላይ ሲሰቡለት ከአንድ ደግ ኢትዪጵያዊ ደግሞ አንድ ራሱን
         የቻለ  መኖሪያ  ቤት  አቶ  ማርቆስ  በህይወት  እስካለ  ድረስ  የሚኖርበት  ቤት
         ለግሰውታል።

         ማህበረ  ረድኤት  እና  አሰባሳቢው  ኮሚቴም  አቶ  ማርከስ  የተሰበሰበው  ገንዘብ
         በተለያዩ ምክንያቶች በቀጥታ ለአቶ ማርከስ መስጠት ስላልቻሉ በአቶ ማርቆስ
         እና በአሰባሳቢው ስምምነት በአካባቢው ካሉት የሃይማኖት ተቁዋማት በቅርብ
         ያለውን  የአቡነ  ገብረመንፈስ  ቅዱስ  ቤተክርስትያን  ገንዘቡን  በሞግዚትነት
         እንዲያስተዳድሩለት  የቤተክርስትያኑ  አስተዳደር  እና  ሰበካ  ጉባኤ  በጹሁፍ
         ጠይቀው ቤተክርስትያኑም ጥያቄውን ተቀብለው አስተናግደዋል።
                                                                                                         09/30/2020
                                                                                                        Johns Hopkins University
          በዚህም መሰረት ማህበረ ረድኤት  ለቤተክርስትያኑ ገንዘቡን ሲያስረክብ ለአቶ
         ማርቆስ   በየወሩ   የተወሰነለትን   ገንዘብ   ብሩ   እስኪያልቅ    ድረስ
         በየወሩ    የተወሰነለትን  ብር  ሊሰጡት  ፣በአጋጣሚ  አቶ  ማርቆስ  ከዚህ  አለም
         በህይወት ቢለይ ቀሪውን ገንዘብ ኢትዮጽያ ላለው መቆደኒያ ለተባለው ድርጅት
         እንዲሰጥ በሚል ተስማምተው ስራቸውን አጠናቀዋል።

         በዚህ  አጋጣሚ  ማህበረ  ረድኤት  ለዚህ  በጎ  ነገር  የተባበሩትን  ሁሉ  እያመሰገነ
         በተለይም  የመኖሪያ  ቤቱን  ለሰጡት፣  መኖሪያ  ቤቱን  ለአደሱት  ግብረ  ሃይሎች
         እንዲሁም  ለአቡነ  ገብረ  መንፈስ  ቅዱስ  ቤተክርስትያን  አስተዳደር  ከልብ
         ያመሰግናል።

         ማህበረ ረድኤት ማህበር የአሜሪካን ህግን በተከተለ 501C ደረጃ ያለው ህጋዊ
         ድርጅት  ነው።  በማህበረ  ረድኤት  በኩል  የረዱትን  እርዳታ  ታክስዎን  ሲያሰሩ
         ማስቀንስ ይችላሉ። በማንኛውም ጊዜ በድርጅቱ ድረ ገጽ
         (https://www.mahbereredeat.org)
         በመግባት ይርዱ።
                                                                                                   Source: MoH  Ethiopia






        66                                                                                  “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር ”                                                          ድንቅ   መጽሔት -  ጥቅምት  2013
   61   62   63   64   65   66   67   68   69   70   71