Page 4 - Ethiopia in the Bible by Abune Petros 2
P. 4

መጽሐፍ  ቅዱስ  ኢትዮጵያ  የሚለውን  ስም  የተጠቀመበት  ምክንያቱ  ምንድን  ነው  ?  የሚለውን  ጥያቄ  በቦታው
        እንመለከተዋለን ።

             በዚህ ቦታ ላይ ግን ለዚህ ጽሑፍ አነሣሽ ምክንያት የሆነው ዐቢይ ጉዳይ በጀርመን ሀገር በተካሄደ የመጽሐፍ ቅዱስ
        የትርጉም ሥራ ውስጥ ኢትዮጵያ የሚለው ቃል እንዳይኖር የመደረጉን አግባብነት ከክርስትና ሥነ መለኮት ፣ ከሥነ ልሳንና
        ከታሪክ አኳያ መዝኖ ማየት ነው ።

             በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ በጀርመን የሥነ መለኮት ትምህርታቸውን ተምረው የዶክትሬት ድግሪ መመረቂያ ሥራቸውን
        የሠሩ ዶክተር በንቲ ኡጁሉ የተባሉ ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ፥ የጀርመን ወንጌላዊት ሉተራን ቤተ ክርስቲያን ባሳተመችው አዲስ
        የጀርመንኛ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኢትዮጵያ የሚለው ስም እንዳይኖር የተደረገው ኢትዮጵያ የሚለው ስም ስድብ ስለ ሆነ
        ነው ብለው ተናግረዋል ።


             እንደ እርሳቸው አባባል ከአርባ አምስት ጊዜ በላይ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰው “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃል በሙሉ
        ትርጉሙ ኩሽ መባል አለበት ፤ ሌሎቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞችም የትርጉም ሥራቸውን በሚያሻሽሉበት ጊዜ ይህንኑ
        ፈለግ መከተል አለባቸው ይላል ። ይህን ሐሳባቸውንም እንዲህ ይገልጡታል ። “የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ከመካከለኛው
        ዘመን ጀምሮ እየተካሄደ ያለ ነገር ነው ። ከየትርጉም ሥራው ጀርባ ያለው ሐሳብ በቀድሞዎቹ ኅትመቶች ውስጥ የተወሰኑ
        ጉድለቶችና ግድፈቶች ይኖራሉ” ከእነዚህ ስሕተቶች አንዱ ደግሞ በዕብራይስጡ ኩሽ ተብሎ የቀረበው ወደ ግሪክ ሲተረጎም

        ኢትዮጵያ ተብሎ መተርጎሙ ነው ።

             የተለያዩ  የመጽሐፍ  ቅዱስ  ማኅበራት  መጽሐፍ  ቅዱስን  ሲተረጉሙ  ኑረዋል  ።  ይህ  የመጀመሪያ  ጊዜ  አይደለም  ።
        በአሥራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን ማርቲን ሉተር መጽሐፍ ቅዱስን ከላቲን ወደ ጀርመንኛ ከተረጎመበት ጊዜ ጀምሮ የቋንቋና
        የሐሳብ  ትርጉም  እየተካሄደ  እንዳለ  ነው  ።  በነዚያ  ትርጉሞች  ውስጥ  ስህተቶች  ነበሩ  ።  አንዳንዶቹ  የቋንቋ  ሌሎቹም
        ግንዛቤያዊ ነበሩ ። አሁን እየተካሄደ ላለው ትርጉም ምክንያቱ እነዚያ ያለፉ ስህተቶች ናቸው” ይላሉ እኔሁ ሊቅ ።


             ይህ ሲገባን ነው የዶክተር በንቲ ኢትዮጵያን ከመጽሐፍ ቅዱስ ማውጣት እንዴት ትክክል ነው እንደሚሉ መረዳት
        የምንችለው  ።  ክፍሉን  እንደምንመለከተው  ከሉተር  የፕሮቴስታንት  እንቅስቃሴ  ጀምሮ  የመጽሕፍ  ቅዱስ  ትርጉሞች
        እየተካሄዱ ነው ። የዚህ ሥራ ምክንያትም በቀድሞው የጀርመንኛ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙትን “የቋንቋ ስሕተቶች”
        ለማረም ሲሆን ፤ ምክንያቱም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አግላይ ቃላት መኖር የለባቸውም የሚል ነው ።


             ይህ አባባላቸው የዶክተር በንቲ የሥነ መለኮት ቅኝት ለዘብተኛ ሥነ መለኮት (Liberal Theology) የሚባለው
        መሆኑን  በሚገባ  ያመለክታል  ።  ለዘብተኛ  ሥነ  መለኮት  መጽሐፍ  ቅዱስን  የሚመለከተው  እንደ  አንድ  ከፍተኛ  ስፍራ

        የሚሰጠው ባህል ወለድ ሥነ  ጽሑፍ  (Literary Cultural production) አድርጎ  ነው ። ክርስትናንም የባህል

        አንጻራዊነትን  (Cultural relativism) በተተገነ መንገድ  ብቻ ለማብራራት ይሞክራል ። ግብረ ገባዊ ዕሤቶችንም
        ከሃይማኖት  ገንጥሎ  በራሳቸው  ለማቆም  ይሞክራል  ።  ለዘብተኛ  ነገረ  መለኮት  ዘመናዊውን  ዓለም  ክርስቲያን  ከማድረግ
        ይልቅ ክርስትናን ከዘመኑ መንፈስ ጋር ለማስማማትና በዘመናዊ ሰዎች ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ ይጣጣራል
        ። ለዚህ ሲል ከሐዋርያዊ የክርስትና ትምህርት በእጅጉ የራቀ ፣ ከቤተ ክርስቲያን ትውፊት የተፋታ የግብረ ገብ አስተምህሮ

        ያስተምራል ።

             ለምሳሌ ፦ በዘመናችን ያለውን የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ፖለቲካዊ ዕውቅና እንዲያገኝ የማድረግ ዘመቻ ክርስቲያናዊ
        ጭምብል ለማልበስ  ይሞክራል ። ለዘብተኛ ሥነ መለኮት ፣ ሲያሻው መጽሐፍ ቅዱስ  ተመሳሳይ  ጾታ አያወግዝም ብሎ
        የዐይነ ደረቅ ክርክር ያቀርባል ። ክርክሩ አላዋጣ ሲል ደግሞ ጭራሽ “የተመሳሳይ ጾታ ፍላጎት ላላቸው ሰዎች የሚስማማ
        መጽሐፍ ቅዱስ” እስከ ማዘጋጀት ይደርሳል ። ለዚህ ሁሉ ክሕደት የሚቀርበው ምክንያትም  እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ

        ስለሚወድድ ማንንም የሚያገልል ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መኖር የለበትም የሚል ነው። የዘመኑን ሰዎች ለማስደሰት
        ሲል  የእግዚአብሔርን  እውነት  ፣  የሐዋርያትን  ትምህርት  ፣  የአበውን  ምስክር  ፣  የቤተ  ክርስቲያንን  ትውፊት  በሙሉ
        አሽቀንጥሮ ይጥላል ።


         “.ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች።”   መዝሙረ ዳዊት - ም. 68 ቁ. 31                                                          4
   1   2   3   4   5   6   7   8   9