Page 9 - Ethiopia in the Bible by Abune Petros 2
P. 9
እኅቶቹ ሃያ ስምንት ልጆች ወልዷል ። ዕድሜውም አራት መቶ ሰባ ስምንት ነው ። መዲናውና መቃብሩ አኩስም ናት
ይላል ። ሃያ ስምንት ያላቸውንም በየስማቸው እንደ ተጻፉ በማስረጃ አቅርበዋል ። ዘፍ 10 ፥ 7 ፥ 8 ።
ከዚህ በተጨማሪ የተጠቀሰው ነገድ አቢስ እንጂ ኢትዮጲስ የተባለ ነገድ የለም ፣ ይላሉ አለቃ ። አለቃ
ሐተታቸውን በዚህ አያቆሙም። ኢትዎፕስ የሚለው በጽርዕ ሁለት ትርጉም እንዳለው ነው የሚነግሩን ። ይኸውም
አንደኛው የሰው ስም ፥ ሁለተኛው የአገር ስም ። ሐሳባቸውን ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ ፦
የሰው ስም ሲኾን ጥቍር ጠቋራ ክሰልማ ። የሀገር ስም ሲኾን ፥ ቈላ ፥ በረሓ ፥ ምድረ በዳ ። ስምነቱ ከኩሽ
ሞት በኋላ በሁለት ሽሕ አራት መቶ ሃምሳ ዓመት ሰብአ ሊቃናት ያወጡት ከ፸ ሊቃናት የተገኘ ሐዲስ እንግዳ ደኃራዊ
ስም ነው ። በሱዳን ዙሪያ ያለችውም መላይቱ አፍሪቃ ይልቁንም ከነጭ ዓባይ ወዲህ ያለችው ክፍል ፣ የጥቍሮች
የኩሽ ልጆች አገር ስለ ሆነች በዚህ በአዲሱ ስም ኢትዮጵያ ትባላለች ። ዘፍ 2 ፥ 13 ።
በብሉይ በሐዲስ የተጻፈው ዋነኛውና መደበኛው “ኢትዮጵያ” ግን ታላቁን በረሓ ሰሐራን ጨምሮ የኖባ ክፍል
ነው ይላሉ ። 2ዜና 14 ፡9 ፡12:13 ። 16 : 8 ። 4ነገ 19 ፥ 9 ። ኢሳ 37 ፥ 9 ። ሕዝ 30 ፥ 5 ። ግብ 8 ፥ 27-39 ። (ገጽ
248)
በዚህ የመዘገበ ቃላት ማስረጃ መሠረት ኢትዮጵያ የሚለው ስም ሁለት ትልልቅ ክፍል ያለው ነው። የሰው ስም
ሲሆን ኩሽ የሚለውንና ጥቍር የሚለውን ያመለክታል ። የሀገር ስም ሲሆን ደግሞ ቆላ ከነጭ ዓባይ በመለስ ኑብያን
ይዞ ያለውን አገር ያሳያል ። የሰሓራን በርሓ የሚያካትት ስለ ሆነ ምን አልባትም እስክ ሕንድ ውቅያኖስ ያለውን
መልክዐ ምድር ያጠቃልላል ማለት ነው ።
ከዚህ በተጨማሪ የሰብአ ሊቃናት ትርጉም ዕብራይስጡ ኩሽ ያለውን ኢትዮጵያ ብለው መተርጎማቸው
ትክክለኛ የመንፈስ ቅዱስ እጅ ያለበት አሠራር ነው እንጂ የተሳሳተ ትርጉም ሊባል አይቻልም ። ምክንያት ኩሽ
የሚለው የዕብራይስጥ ቃል በግሪኩ የተገኘለት አቻ ቃል ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ነውና ። የሰባ ሊቃናቱ ትርጉም
ይህንን ቃል ሲሰጥ እንደ አሁኑ የፖለቲካ ንትርክ በሌለበትና በእግዚእብሔር መንፈስ መሪነት በሆነ ሥራ ብቻ እንጂ
አሁን የሕሊና ቀውስ ውስጥ በገቡ የተገንጣይ ፖለቲካ አቀንቃኞች ገፋፍተዋቸው ፥ በሊቅ ስም የሚነግዱ ፊደል
የቆጠሩ ፥ ግን ደግሞ አመዛዛኝ አእምሮ የሌላቸው ሰዎች አልነበሩም ።
ምንስ ጥቅም ሊያገኙ ይህን ታላቅ ነገር ለዘር ወይስ ለስድብ ወይም አንድን ማኅበረ ሰብ ለማዋረድ ሌላውን
ለማንገሥ ሊያደርጉት ይችላሉ ? የአንድን ቃል ትርጉም አቻ ቃል ከማግኘት ያለፈ ጉዳይ አላቸው ብሎ ማመን
የእግዚብሔርን ቃል መቃረን ይሆናል ።
አርባ አምስት ጊዜ የተጠቀሰው ኢትዮጵያ የሚለው ቃል የጥቁር ሰው ስም ወይም ኩሽ ብቻ አይደለም ።
ኢትዮጵያ የሚለው ስም የተደራጀ መንግሥት ያለው አገርና ሕዝብ ማለት ነው ።
ዶክተር በንቲ ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ስድብ ነው ፥ በጣም ያናድደኛል ነው የሚሉት ። የተናደዱበትን ሐሳብ
እንዲህ ነው የሚገልጡት ፦
ማናቸውም ቤተ ክርስቲያን እኔን ቢሰድበኝ ቤተ ክርስቲያኔ አልለውም ። ይህ የማንነት ጉዳይ ነው ። አባትህ
ያወጣልህ ስም በባዕዳን ቢለወጥ ያናድድሀል ። ማንነትህን ባህልህን ሁሉ ያወድመዋል ። እዚህ የሆነው ነገር በትክክል
ይህ ነው ። የኩሽ ሕዝቦች ራሳቸውን የተቃጠለ ፊት ብለው አይጠሩም ። ኦሮሞ ፥ ሶማሌ ፥ አፋር ፥ እና ሌሎችም
የኩሽ ሕዝቦች መሆናቸውን ታሪክ ይነግረናል ። አንድም የገባው የተገለጠለት የኩሽ ሰው ፥ ግሪኮች ለኛ በሰጡን
ክብረነክ አዋራጅ ስም ደስተኛ አይደለም ። የመጀመሪያው ስማችን ኩሽ መጠሪያችን እንዲሆን መልሰን ለመጠየቅ
ደስተኞች ነን ። ስለዚህ ለውጡ ይህ ነው ። እንዳለ የኩሽ ሕዝቦችን ታሪክ በትክክል ሊቀይረው ይችላል ። የኩሽ
ሰዎች ቋንቋዎች አሏቸው እና የሚኖሩበት መልክአ ምድራቸውም በደንብ የታወቀ ነው ። ግን ኢትዮጵያ ከሚለው ቃል
ጋር የሚዛመድ ሕዝብም ፥ ቦታም ፥ ቋንቋም የለም ። ባንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች የኢትዮጵያ ጥናት እንዳለ እሰማለሁ ።
መጨረሻ ላይ ይሄም ይቀየራል ። ምክንያቱም ጥያቄ ያስነሣል ። ኢትዮጵያ ማነው ?ኢትዮጵያ ምንድነው ?
ከላይ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከአርባ አምስት ጊዜ በላይ ተጠቅሶ አገኘሁ ብለው ፥ ያንን ለማስወጣት ትልቅ
“.ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች።” መዝሙረ ዳዊት - ም. 68 ቁ. 31 9