Page 13 - Ethiopia in the Bible by Abune Petros 2
P. 13

ዶክተር ላጲሶ ብዙ ጠቃሚ ነጥቦችን አንሥተዋል ። የመጀምሪያው በአፍሪካ ቀንድ የኖረና የሚኖረው ሕዝብ በሙሉ
        የተፈረጀው ኩሽ በሚለው ስም ብቻ ነው ። ይህ ደግሞ ሌላ አፍሪካዊ ከለር የለም ፣ ሌላ አፍሪካዊ ከለር ካለም ከውጭ

        የመጣ ነው የሚል ይሆናል ። ሁለተኛው ነጥብ ይህን ስም የሰጡ ዘረኛ ነጮች በተለይም የጀርመን ሥነ ልሳን አጥኚዎች
        ናቸው  ።  ሦስተኛው  ነጥብ  የጀርመኖቹ  የታሪክ  ፍልስፍና  የሰው  ዘር  የተገኘው  በመካከለኛው  ምሥራቅ  ነው  ፣  ይህ
        በመካከለኛው ምሥራቅ የተገኘው ሰውም ዘሩ የተለየ ነው የሚል የተሳሳተ የታሪክ ግንዛቤ አስጨብጠዋል የሚሉት ዋና
        ዋናዎቹ ናቸው ።

              ይህን ያደረጉት አሉ ዶክተር ምዕራባውያን ነጭ የታሪክ ምሁራን የኢትዮጵያንና የግብጽን የኑብያን ሥልጣኔ በመካድ

        ነው ። ይህም ጥቁር አይሠራም ፥ ሥልጣኔም የለውም ለማለት ያደረጉት ሴራ ነው ። በዚህ ተነሥተው አሉ ዶክተር ላጲሶ
        “የግብፅ ፥ የኑቢያ ፥ የኢትዮጵያ ሥልጣኔዎች መጤዎች ናቸው ብለው አስተማሩ ።

              ከዚህ  ነጥብ  ላይ  እንደ  ዶክተር  በንቲ  የሕሊና  ቀውስ  የመጣው  የዶክተር  በንቲ  አስተማሪዎች  የሚያውቁትና
        እንዲታወቅ  የሚፈልጉትም  ይህኑ  በዘረኝነት  የተመረዘ  የዘር  ሱስ  ፍልስፍና  ነው  ።  የእኛውን  ዶክተርም  ይህንኑ  ግተው
        ራሳቸውን እንዳያውቁ ከዚያም ሲያልፍ እንዲጠሉ አድርገው አስተምረዋቸዋል ።


              ዶክተር  ላጲሶ  አቢሲንያ  ተብሎ  የመጠራት  አባዜ  የመጣውም  ከምን  እንደ  ሆነ  ያብራራሉ  ።  የመጀመሪያ
        የአውሮፓውያን  የዘረኝነት  መሠረት  የተነሣው  ጥቁር  ሰው  አይደለም  ከሚል  ከንቀት  ነው  ።  ይህም  የግሪክ  ሥልጣኔ
        ከግብጽና ከኑብያ  አልመጣም ለማለት ይሞክራል ።  ሁኖም የሦስቱ ጥቁር ሕዝብ ሥልጣኔዎች የነሱ የሥልጣኔ ምንጭ
        መሆናቸውን  አግኝተዋቸዋል  ይላል  ።  ይህ  ግኝት  አውሮፓውያንን  ከአጣብቂኝ  ውስጥ  ስላገባቸው  አንድ  ዘዴ  መቀየስ
        ነበረባቸው ። ይህንም ሲቀጥሉ ዶክተር እንዲህ አሉ ፦


              ስለዚህ  አውሮፓውያን  ከፍተኛ  አጣብቂኝ  ውስጥ  ገቡ  ፣  በመግባታቸውም  ኢትዮጵያ  የሚለውን  ስም  በመፋቅ
        አቢሲኒያ በሚል ስያሜ ተኩት ። የአንድን ነገር ህልውና ለማጥፋት መጀመሪያ መጠሪያውን መቀየር የተለመደ አካሄድ
        መሆኑን ካርል ማርክስ በአጽንኦት መግለጹን እዚህ ላይ ማስታወስ ይጠቅማል” በማለት ገልጸውታል ።

              ለዚህ ጽሑፍ ከዚህ ሌላ መሄዱ አስፈላጊ አይደለም እንጂ እጅግ ብዙ ማስረጃዎች ማቅረብና መተንተን ይቻላል ።
        ዶክተር ላጲሶን የታሪክ ምንጮቻቸውን ፥ የከርሰ ምድር ምርምር ፥ የሥነ ቋንቋ ሥርዐት ፥ የጥንት የምልክት ጽሑፎች ፥

        የቅርብ ጊዜ የግሪክ ፥ የላቲን ፥ እንዲሁም የኢትዮጵያ የነገሥታት ዜና መዋዕሎች ፥ የብራና ጽሑፎች እንደ ሆኑ በአግባቡ
        ገልጸዋል  ።  እነዚህ  ሁሉ  ከላይኛው  ግብጽ  ጀምሮ  እስከ  ህንድ  ውቅያኖስ  ድረስ  የሚሸፍነው  መልክዐ  ምድር  ኢትዮጵያ
        የሚባል አገር እንደ ሆነ፣ በዚህ ውስጥ ልዩ ልዩ ቋንቋ የሚናገሩ ሕዝቦችና መንግሥታት የነበሩ ሲሆን ፥ እነዚህ ሁሉ በአንድ
        ኢትዮጵያ በሚል መጠሪያ የሚታወቅ መንግሥት እንደ ነበረ አብራርተዋል ።

              ከጥንት  ጸሐፍያን  በአምስተኛው  ክፍለ  ዘመን  (ከክርስቶስ  ልደት  በፊት)  የነበረው  ሔሮዶቱስ  የተባለው  ጸሐፊ
        ኢትዮጵያ  ስለሚባል  አገር  ሕዝብና  መንግሥት  በሰፊው  ዘርዝሯል  ።  The  Land  mark  Herodotus:  The

        Histories በተሰኘው ባለ ዘጠኝ ቅጽ መጽሐፍ ቅጽ ሦስት ላይ ያለውን እንመልከት ።


              ሔሮዶቱስ የብሉይ ኪዳን ተርጓሚዎች የነበሩትን ሰብዐ ሊቃናት በመቶ ዓመት ይቀድማቸዋል ። ይህ ሰው ትረካውን
        የሚጀምረው  የፐርሽያ  ወራሪ  ንጉሥ  ኢትዮጵያ  የሚባል  አገር  እንዲሰልሉለት  በሚልካቸው  መልእክተኞቹ  ነው  ።
        የፐርሽያው ጦረኛ ንጉሥ ሰላዮች እንደ አሁኖቹ ሰላዮች ሁሉ ውሸታሞች ነበሩ ። ውሸታቸው ለሚሰልሉት ለኢትዮጵያ
        ንጉሥ ስጦታ ይዘን መጥተናል በማለት አታለው እንደ ሆነ ሔሮዶቱስ ይተርካል ። ግን በውሸት የሚደልሉ መሆናቸውን

        ኢትዮጵያውያኑ እንደ ደረሱባቸው ዘግቧል ። እነዚህ ሰላዮች ዓሣ በሊዎች ተብለው የተጠቀሱ ሲሆን ፥ ብዙ ስጦታም
        ለኢትዮጵያ ንጉሥ አቅርበዋል ። ግን በመጨረሻ ላይ መዋሸታቸው ከዚያው እንዳሉ ታውቆባቸዋል ።







         “.ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች።”   መዝሙረ ዳዊት - ም. 68 ቁ. 31                                                            13
   8   9   10   11   12   13   14   15   16   17   18