Page 11 - Ethiopia in the Bible by Abune Petros 2
P. 11
የሚያስፈራ ታላቅ አገር ሲሆን ፥ ዋና ከተማውም “ሜሮ” እንደሚባል ገልጿል ።
ዶ/ር በንቲ ያላቸው የተሳሳተ የታሪክ ግንዛቤ በሚከተለው ንግግራቸውም የሚታይ ነበር ። ለአንባቢ ይረዳ ዘንድ
ጥያቄውን በሙሉ አስፍረነዋል ፦
ጥያቄ ፤ በኢትዮጵያ በትምህርት ላቅ ባሉ (elite) ክፍሎችም ሆነ በሌላው ማኅበረሰብ ዘንድ ማንነትን በተመለከተ
የተጋጋሉ ክርክሮች ይስተዋላሉ ። ብቸኛው ማንነታችን "ኢትዮጵያዊነት" ነው ብለው የሚከራከሩ አሉ ። በሌላው በኩል
ደግሞ ቀዳሚው የጎሳ ማንነታችን ነው ፣ ኢትዯጵያዊነት ሁለተኛ ደረጃ ነው ብለው የሚከራከሩ አሉ ። ሌሎች ደግሞ
ጭራሽ ባጠቃላይ ኢትዮጵያዊ ማንነትን የማይቀበሉ አሉ ። ለዚህ አነጋጋሪ ለሆነው የማንነት ጉዳይ ይህ አዲሱ ትርጉም
አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለው ያስባሉ ?
ማለት በቀላል አባባል ላስቀምጠው ብል ይህንን ብቸኛ ማንነታችን ኢትዮጵያዊ ነው ለሚሉና ለዚህ ተቃራኒ ለሆኑ
ሰዎች ይህ ትርጉም የሚሰጠው ፋይዳ ምንድ ነው? እንደ ማለት ነው ።
መልስ እውነት ነጻ ያወጣሃል ብየ አስባለሁ ። የመጀመርያው ስም "ኩሽ" ለመሆኑ ማስረጃ እስካለ ድረስ ቃሉ
"ኢትዮጵያ" ነው ብሎ የሚያከራክር ምክንያት የለም ። "ኢትዮጵያ" ብለው ሊጠሩን ያስቻላቸው ሳይንሳዊ ማስረጃ
አያገኙም ይሆናል ። ሳይንሳዊ ስል የአርኪዎሎጂ የሥነ ቋንቋ እንዲሁም የታሪክ ማስረጃዎችን ማለቴ ነው ። አሁን
ስላለችው ኢትዮጵያ ታሪክ እንድነግርህ ፍቀድልኝ ። ከ1900-1908 እስከዚህ ጊዜ ድረስ የዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ሥነ መልክዐ
ምድር (ካርታ) አልነበረም ። ከዚያ በፊት ሕዝቡ ኦሮሞ ፤ አማራ ፤ ሲዳማ ፤ አፋር ፤ ትግሬ ወዘተ. ይባሉ ነበር ። አሁን
ያለችው ኢትዮጵያ ካርታ ዳር ድንበር የተቋቋመው ፤ የተመሠረተው ፤ በዳግማዊ ምኒልክ የአቢሲኒያው ንጉሥ ነው ።
የደቡብን ኩሾችና ሌሎችንም በቅኝ የያዘውና አሁን ያለችውን ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር ግዛት የፈጠረ ። እስከ 1931
ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ሕጋዊ እውቅና አላገኘም ነበር ። ከ1931 ዓም በፊት ሀገሪቱ አቢሲኒያ ነበር የምትባለው ። እና
አቢሲኒያውያን ራሳቸውን የሴም ሕዝብ ብለው ነው የሚጠሩት ። ንጉሥ ኃይለ ሥላሴ ናቸው በ1931 ዓም በመጀመሪያ
ሕገ መንግሥታቸው ውስጥ አቢሲኒያ የሚለውን ስም ጥለው ኢትዮጵያ የሚለውን ስም ያጸደቁት ።
ለእውነት የቆሙ የሚመስሉት ዶክተር በንቲ ይህን አስጨናቂ ጥያቄ ለመመለስ የጀመሩት ብልጥነት የተሞላበት
አባባል ፥ ግን ደግሞ መሬት የለቀቀ ውሸትን ለመዋሸት ታላቁን ቃል እውነትን ተግባሩን ሳይሆን ቃሉን ብቻ ተጠቅመው
“እውነት ነጻ ታወጣችኋለች” አሉ ።
እውነት ዶክተር በንቲ እውነተኛ ሰው ናቸውን ? የተጠቀሙትን ቃል ተገንዝበውት ይሆንን ? እውነት እኮ
የሚጨበት የሚዳሰስ የሚታይ ነገር ነው ። እንደዚህ ቢያንስ በመቶ የሚቈጠሩ ዓመቶችን የሚታይ የሚጨበጥ
የሚዳሰሰውን ጉዳይ እኮ ነው “ኩሽ ለመሆኑ ማስረጃ እስካለ ድረስ ኢትዮጵያ ነው ብሎ የሚከራከር ማንነው” የሚሉት ።
ደግሞም የአርኪዎሎጂ ማስረጃ የሚሉት ዶክተር እስከ አሁንም የሚያምኑት በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ኢትዮጵያ
የሚለው ቃል በሙሉ ኩሽ ነው መባል ያለበት ብለው ነው ። ከዚያ ሲያልፍም ኢትዮጵያ የሚለው አገር እንደ አገር
የተመሠረተው በአቢሲኒያው ንጉሥ በአጼ ምኒልክ እንዲያውም ሀገሩ የተከለለው በአጼ ኃይለ ሥላሴ ነው እያሉን ነው ።
እንዴት ያሳፍራል ! ያሳዝናልም ! አስገራሚም ነገር ነው !! ይህ መከረኛ ክርስቲያንነት የሁሉም የውሸት ምሽግ ሁኖ
እያገለገለ ይገኛል ። እኔ ክርስቲያን ነኝ ፥ አገልጋይ ነኝ ፥ እውነተኛ አገልጋይ መሆን አለብኝ ማለታቸው እሚገርም ነው ።
ኢትዮጵያ የሚለው ስም ከመውጣቱ በፊት አማራ ፥ ትግሬ ፥ ኦሮሞ፥ አፋር ነበር የሚባለው ይሉናል ።
እኛም እኮ መጽሐፍ ቅዱስ ከመጻፉ በፊት እነዚህን ሕዝቦች ያካተተ ኢትዮጵያ የሚባል አገርና መንግሥት ነበር
ነው የምንለው ። ይህ ከዚህ በላይ በመጠኑ የተመለከትነው ከሥነ ልሳን አንጻር ሲሆን ። አሁነ ደግሞ ይህ ኢትዮጵያ
የሚለው ስምና አገር ከታሪክ አንጻር ምን ይመስላል የሚለውን እንመልከት ።
“.ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች።” መዝሙረ ዳዊት - ም. 68 ቁ. 31 11