Page 6 - Ethiopia in the Bible by Abune Petros 2
P. 6
በንቲ በሥነ ልሳን ሚዛን ላይ
ዶ//ር በንቲ ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም በየጊዜው ተስተካክሏል ፣ የማስተካከሉ ሂደትም የሚያካትተው የስምም
የግንዛቤም መስተካከል ነው ። አሁንም በመካሄድ ላይ ነው ይላሉ ። እርሳቸው እንደሚሉት ፦ የግንዛቤና የሐሳብ ልዩነት
ካለበት መጽሐፍ ቅዱስ እስክ አሁን እየተመራንበት ያለው በስህተት ነው የሚሉትን ሐሳብ እንመልከተው ፦
“ግሪኮች ብሉይ ኪዳንን ከሂብሩ ቋንቋ ወደ ግሪክ ሲተረጉሙ "ኩሽ" የሚለውን ወደ "ኢትዮጲስ" በመቀየር ስህተት
ሠሩ ። ኩሽ የጥቁር አፍሪካ ሕዝብ ስም ነበር ወደ ኢትዮጲስ ተለወጠ ። ትርጉሙ "ፊቱ የተቃጠለ ሕዝብ" ማለት ነው ።
ኩሽ በመሆንና የተቃጠለ ፊት በመሆን መካከል ትልቅ ልዩነት አለ ። ጥቁር ሕዝቦች ፊታቸው የተቃጠለ አይደለም ።
ጥቁሮች ናቸው በቃ ። ይህ አዲሱ በጀርመን ኢቫንጀሊካን ሉተራን ቸርች በ2017 የታተመው መጽሐፍ ቅዱስ እነዚያን
ስሕተቶች በማረም ነው ማለት ነው” ።
ይህንን ገለጣ ከተቀበልነው በእርሳቸው አባባል የጀርመን ሉተራን ኢቫጀሊካን ቸርች ያረመው ስህተት ኢትዮጵያ
የሚለውን ስሕተት ኩሽ በማለት ማስተካከል ነው ። ታረመ የተባለው ይኽ ነው ማለት ነው ። ለዚህ አመለካከት
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ለዚሁ ጽሑፍ የሰጡት መልስ አጥጋቢ ነው ብለን እናስባለን ፣ እርሳቸው ለዚህ ጽሑፍ የሰጡት
መልስ በኢትዮ ሚድያ ድኅረ ገጽ ከወጣው የሚከተለውን አብረን እንመልከተው ፦
“እነዚህ ሰባ (ሁለት) ሊቃናት ሲተረጉሙ ፥ ዕብራይስጡ ብሉይ ኪዳን ውስጥ የሀገርና የሕዝብ ስም ሲያጋጥማቸው
አንዳንዱን ዕብራይስጡ ውስጥ እንዳለው ይወስዱታል ። አንዳንዱን ፥ ለምሳሌ እንደ “ኹሽ” እንደ “ፍልስጥኤም” ያሉ
ስሞችን እንዳለ በመውሰድ ፈንታ ፥ የግሪክ ተመሳሳይ ስም ይሰጡታል ። (ፍልስጥኤምን “ኢሎፍሊ” ፥ ኩሽን “ኤይቲኦፕ”
አሏቸው) የዕብራይስጡ “ኩሽ” የሚያመለክተው ጥቁርን ሕዝብ ነው ። ግሪኮች ደግሞ ጥቁሩን ሕዝብ የሚጠሩት
“ኤይቲኦፕ” ብለው ስለ ሆነ ፥ “ኩሽ” የሚለውን ስም “ኤይቲኦፕ” ቢሉት አይገርምም ። ባጭሩ ፥ ግሪኩ “ኤይቲኦፕ”
የሚላቸው ዕብራይስጡ “ኩሽ” የሚላቸውን ሕዝቦች ነው”
ይህ በንቲ ኡጁሉ አንደኛ “ኢትዮጵያ” ማለት በዚያ ዘመን ግሪኮቹ ጥቁርን ሕዝብ የሚጠሩበት የማንኛውም ጥቁር
መጠሪያ ነው ። ከዚያ ሲያልፍም በግብፅ በስተደቡብ የሚገኙ ሱዳኖችና ኢትዮጵያውያንን አንድ አድርገው ኢትዮጵያ
ብለው ነው ።
ከዚህ በላይ እንደምንመለከተው የሰብዐ ሊቃናት ትርጉም የሕዝብና የሀገር ስም ሲገኝ አንዳንዱን ስሙን አንዳለ
ወስደውታል አንዳንዱን ግን እነርሱ ይቀርባል ያሉትን የስም ትርጉም ሰጥተውታል ። እርግጥ ነው ፣ ዕብራይስጡ የሚለው
“ שׁוּכ ኩሽ” ነው ። ፍቺውም ከምድረ ፍልስጥኤም በስተደቡብ ፣ ከላዕላይ ግብፅ ወይም ከደቡባዊ የናይል ሸለቆ ጀምሮ
1
2
የሚገኝ ሕዝብ ማለት ነው። ይኽንን የዕብራይስጡን ፍቺ የዕብራይስጥ ቅርብ የኾነው ሱርስትም ይጋራዋል። ይኽንን
የቆዳ መልኩ ጥቁር የኾነ ፥ ሀገር ፥ መንግሥት አቋቁሞ በደቡባዊ የናይል ተፋሰስ የሚኖር ሕዝብ ደግሞ ግሪኮቹ
3
“አይቶፒዮስ” ብለው ይጠሩት ነበር። ከራሳቸው ውጪ ያለውን ዓለም “ባርቤርያን” ብለው ለመጥራት ያልሰነፉት ኩሩዎቹ
ጥንታውያን ግሪኮች ይኽንን ሕዝብ በሚመለከት የነበራቸውን አመለካከት ስናይ ዶ/ር በንቲ እንደሚሉት ቃሉ የስድብ
ሁኖ አናገኘውም ። ለዚኽም ኢትዮጵያውያንን አማልክት የሚወዷቸው ሕዝብ አድርገው የሚያቀርቡት የሆሜር ቅኔዎች
ምስክሮቻችን ናቸው ።
በንቲ እንደሚሉት “ኢትዮጵያ” ማለት በፀሐይ የተቃጠለ ፊት ማለት ስለ ሆነ ጥቁርን ሕዝብ ለመስደብ የተሰነዘረ
ቃል አይደለም ። “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃልም አንድ የተለየ ጥቁር ሕዝብ መጠሪያ አይደለም ። ይልቁንም በጠቅላላ
ከዓባይ ከላይኛው ግብጽ ጀምሮ ያለ ሕዝብ ማለት ነው ። በሌላ አባባል፣ በዚያ ዘመን ግሪኮች ግንዛቤ “ኢትዮጵያ”
የሚለው ቃል የተለያዩ ሕዝቦች የሚኖሩበት ፥ ግን በአብዛኛው ጥቁር ሕዝብ የሚኖርበት ምድር ማለት ነው ።
የአዲሱን መጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም የሠሩት ጀርመናውያን ሊቃውንት ብሉይ ኪዳንን የመለሱት ከግሪክ ሳይሆን
ከዕብራይስጥ ነው ። ዕብራይስጡ ደግሞ ቀድሞውንም “ኩሽ” ነው የሚለው ። ስለዚህም በአዲሱ የጀርመንኛ
ትርጉማቸው የዕብራይስጡን ስያሜ ቢጠብቁ ለዕብራይስጡ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂ ያላቸውን ታማኝነት እንጂ ዶ/ር በንቲ
—————————————————
1
Brown, Francis et al. The Brown-Driver-Briggs Hebrew and English Lexicon.Boston, Hendrickson Publishers, 2015
2
Michael Sokoloff. A Syriac Lexicon.Piscataway, Gorgias Press, 2006.
3
Liddel, Henery and Scott, Robert.A Greek- English Lexicon.Oxfrod, Clarendon Press,1940
“.ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች።” መዝሙረ ዳዊት - ም. 68 ቁ. 31 6