Page 39 - Ayinie Magazine
P. 39

ግጥም
                   ለሰው መድረስ!





                              ወጋየሁ ፈጠነ
                                የብሌን ንቅለ ተከላ የተደረገለት ወጣት

                   ተስፋን የናፈቀ - ፍቅርን የተጠማ
                   ዕንባው ያልደረቀ - ትንሳዔን ያልሰማ
                   ቅኝቱ ምን ይሆን - የወገኔ ዜማ፤


                   ቅኝቱማ እንደሰው - ኩራትን ተላብሶ
                   የርቀት ውጥኑ - እንዳይቀር ደፍርሶ
                   መኖር ህልሙ ነዋ - ጎጆውን ቀልሶ
                   ከወጋ ወጉ ስር - ከተራራው ደርሶ፡፡


                   አትፍራ ተራመድ - ጉልበትህም አይዛል
                   ህልም አለህ እሚፈታ - ጥሪህ ሰሚ አግኝቷል
                   ሩቅ ትደርሳለህ - ቁጭትህ አብቅቷል፤


                   ላንተ ዘብ የቆሙት - የአብራኮችህ ክፋይ
                   ልግስናቸውም - በአደባባይ ሊታይ
                   ይኸው ተሰየሙ - በክብር መዝገብ ላይ፤


                   ራዕይ አንግበው - ተስፋን የሰነቁ
                   በምርምራቸው - ሳይንስን ያወቁ
                   በወግ ማዕረጋቸው - ለሀገር የበቁ
                   ቁስልህ አመማቸው - ላንተ ተጨነቁ
                   ጤና ቢነሳቸው - ጤናህ መታወኩ
                   በሙያቸው ጥረው - በደስታህ ባይረኩ
                   አዲስ ብስራት ይዘው - በርህን አንኳኩ
                   የጨለመብህን - ብርሃን ሊተኩ፤
                   ይኸው ተሰለፉ - ብሌን ሊለግሱ
                   አንድ ሆነው እያለ - ሁለቴ ሊደርሱ፤


                   ይህ ሀቅ ሲመዘን - ይህ እውነት ሲለካ
                   ሀኪም መሆን ማለት
                   ዕድሜ ዘላለምን
                   ለሰው አለሁ ማለት - ፊት መሆን ነው ለካ!!!
   34   35   36   37   38   39   40   41   42   43   44