Page 168 - አብን
P. 168

አብን


             ሕዝብ ወይም 52 በመቶ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን በአሁኑ ጊዜ

             በዓመት  ለሞት  የሚጋለጡት  ተላላፊ  ባልሆኑ  ኅመሞች፤
             አደጋዎች  (የመኪና  አደጋ  ጨምሮ)  እና  ለእነርሱ  አጋላጭ
             በሆኑ  ለምሳሌ  በሲጋራ  ጪስ፣  አልኮል  መጠጥ፣  የሰውነት
             ውፍረት፣ የአካል እንቅስቃሴ ጉድለት፣ ወዘተ. ምክንያት ነው፡፡
             እነዚህና መሰል የዘመናችን የጤና ተግዳሮቶች ደግሞ በአጭሩ
             የጤና  ችግር  ብቻ  ሳይሆኑ  በአጠቃላይ  የአገር  ዕድገትና
             ኢኮኖሚ ችግሮች ናቸው፡፡


             በመሆኑም  እነዚህን  የዘመናችን  ተግዳሮቶች  በአስተማማኝ
             ሁኔታ  ለመቅረፍ  በጠቅላይ  ሚኒሰትር  ወይም  በፕሬዝዳነት
             ጽ/ቤት የሚመራ የዘርፍ መስሪያ ቤቶችን በዘርፈ ብዙ ትብብር
             የሚመራ አደረጃጀት እንዲዋቀር ይደረጋል፡፡ የጤናማ መኖሪያ
             አካባቢን  ለመፍጠር፣  የሥርዓተ  ምግብ  ሁኔታን  ለማሻሻልና
             የሕክምና አገልግሎቶችን በጥራትና ፍትኃዊነት ለሁሉም ዜጎች

             ለማዳረስ የሚያስችል  የተቀናጀ የፖሊሲ  ማእቀፍም  ተግባራዊ
             ይደረጋል፡፡

             የማኅበረሰብ  ተሳትፎ  ማስተባበሪያ፣  ቅስቀሳና  ውትወታ
             (Advocacy)

             ማኅብረስብ  የጤና  አገልግሎትና  ግብዓት  ተጠቃሚ  ብቻም
             ሳይሆን  የጤና  አምራች  እንዲሆን  ይደረጋል፡፡  ማኅበረሰቡ

             የዕለት ከዕለት የጤና አግልግሎትና የጤና ፖሊሲዎች ውሳኔ
             ላይ  ንቁ  ተሳታፊ  እንዲሆን  የቅስቀሳና  የማንቃት  ሥራ
             ይሰራል፡፡


             166    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   163   164   165   166   167   168   169   170   171   172   173