Page 173 - አብን
P. 173

አብን




             የትምህርት እርከን

             ዓለምአቀፍ  ደረጃዎችን  አገናዝቦ፣  አገርአቀፍና  አካባቢያዊ

             ጭብጦችንና  ፍላጎትን  አካቶ  ሥርዓተ-ትምህርቱ  በየደረጃው
             በትምህርት        እርከኖች       መካከል       መወራረስና         መደጋገፍ

             እንዲሁም  ተመጣጣኝነት  /ስታንዳርድ/  እንዲጠብቅ  ሆኖ

             ይዘጋጃል፡፡

               መዋለ-ሕፃናት  ለመደበኛ  ትምህርትና  ለአንደኛ  ደረጃ
                ትም/ት  የሚያመቻች  ሲሆን  ልጆች  እሰከ  6  ዓመታቸው

                ድረስ  እንዲማሩ  ይደረጋል፡፡  የዚህ  ዋና  ዓላማ  ሕፃናት

                እራሳቸውን በአግባቡ እንዲገልጹ፣ ከሌሎች ጋር የመግባባት

                ክህሎትን        እንዲያዳብሩ፣         አካባቢያቸውን         እንዲያውቁ

                የሚያስችል መሰረታዊ የሆነ የትም/ቱ ሥርዓት ይሆናል፡፡
                የአጸደ  ሕፃናት  ትምህርት  በዋናነት  በግሉ  ዘረፍ

                ባለሀብቶች፣         መንግስታዊ         ባልሆኑ       ድርጅቶች        እና

                በኃይማኖት  ተቋማት  የሚያዝ  ሲሆን  እንደ  አስፈላጊነቱ

                መንግስትም የሚሳተፍ ይሆናል፡፡

               አንደኛ  ደረጃ  /የመጀመሪያ  ደረጃ/  ትምህርት  በስድስት
                ዓመት  የሚጠናቀቅ  ሲሆን  ሕፃናት  የመደበኛ  ትምህርት

                መጀመር  ያለባቸው  የ7  ዓመት  ዕድሜ  ሲደረሱ  ሆኖ  ለ6


             171    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   168   169   170   171   172   173   174   175   176   177   178