Page 178 - አብን
P. 178

አብን


                የሚሰበሰበው  ገንዘብ  በየጊዜው  የሚጨምርበትና  ዘላቂነቱ

                የሚያረጋግጥበት ሕጋዊ አደረጃጀትና አሠራር ይፈጠራል።

               የጡረተኞች  አበል  በየጊዜው  ከሚፈጠረው  የኑሮ  ውድነት

                ጋር በሚጣጣም መንገድ ማሻሻያ ይደረግበታ።
               አሁን  በሥራ  ላይ  ያለው  የማኅበራዊ  ዋስትና  ፖሊሲ፣

                የፖሊሲው  ማስፈፀሚያ  ሕጎችና  መዋቅሮች  እንዲሻሻሉና
                በጠንካራ መሠረት ላይ የቆመ የማኅበራዊ ዋስትና ፖሊሲ፣
                አደረጃጃትና አሠራር እንዲኖር ይደረጋል።
                ኢትዮጵያውያን           ሁሉ      የማኅበራዊ        ዋስትና       ቁጥር

                 ይሰጣቸዋል፤  ግለሰባዊ  መረጃቸውም  በዘመናዊ  መረጃ

                 ኣያያዝ በኮምፒውተር ይሰነዳል።

                ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል መኖርም
                 ሆነ     መሥራት፣          እንዲሁም         የመኖሪያና        መስሪያ

                 አካባቢያቸውን  እንደየፍላጎታቸው  መቀያየር፣  መዘዋወርና

                 መወሰን ይችላሉ።

                በሰው  ሠራሽና  ተፈጥሯዊ  አደጋ  የተፈናቀሉ  ወገኖችን
                 መልሶ ለማቋቋም አስፈላጊው  እገዛ ይደረጋል።

                የማኅበራዊ ደኅንነት ዋስትና ጽህፈት ቤቶችን በመክፈት፣

                 አቅም በፈቀደ መጠን ለአረጋውያን፣ ወላጅ ያጡ ህጻናትና

                 የጎዳና      ተዳዳሪዎች        አስፈላጊው        እርዳታና        ክብካቤ

                 ይደረጋል።


             176    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   173   174   175   176   177   178   179   180   181   182   183