Page 181 - አብን
P. 181

አብን


             የፖሊሲ  ፈቃደኘነቱ  የሚገለፀውም  ከምግብ  ዋስትና  ጋር

             ተያያዥነት  ያላቸው  ዘርፎች  በሙሉ  አካታችና  የተቀናጀ
             የፖሊሲ  ዕቅድ  በማውጣት  ዘላቂነት  ባላቸው  ስምሪቶች
             እንዲገቡ  ቁርጠኛ  አመራር  ሲሰጥበት  ነው፡፡  ይህ  ሲሆን
             ከችግርነት  ፈቺነት  አቀራረብ  ወደ  አቅም  ገንቢነት  መሸጋገር
             ይቻላል፡፡


             የማኅበረ-ስነ-ምኅዳራዊ  ማእቀፍ  መዋቅር  ሰራሽ  የምግብ
             ዋስትና  ችግሮችን  በዘላቂነት  እልባት  ለመስጠት  ትኩረት
             ሊደረግባቸው የሚገቡ ነጥቦችን ለይቷል፡፡ እነሱም፦


                      አነስተኛ  የእርሻ  ይዞታ  ያላቸውን  አርሶ  አደሮች
                        ከምግብ  ዋስትና  ተጠቂነት  ይልቅ  እንደሁነኛ
                        የምግብ  ዋስትና  ማረጋገጫ  አማራጭ  አድርጎ
                        መመልከትን          የገነገነና     የተንሸዋረረ        ምልከታ
                        መቀየር፣

             መዋቅራዊ ለውጥና ማኅበራዊ ሽግግርን መፍጠር ባልተቻለበት

             ሁኔታ  አነስተኛ  የእርሻ  ይዞታ  ያላቸውን  አርሶ  አደሮች
             እንደምግብ  ዋስትና  ማረጋገጫ  ቁልፍነት  መያዝ  ተገቢነት
             አይኖረውም፡፡  በድምሩ  እጅግ  ሰፊ  የሆኑ  መልማት  የሚችሉ
             የእርሻ  ቦታዎችን  በተበታተነና  በተበጣጠሰ  መልኩ  ከእጅ  ወደ
             አፍ  በሚሆን  ስልተምርት  እያስቀጠሉ  የምግብ  ዋስትናን
             ማረጋገጥ  አይቻልም፡፡  ስለሆነም  አርሶ  አደሮች  ገበያ  ተኮር
             የግብርና  ምርቶችን  በዘመናዊና  የተቀናጄ  መልኩ  እንዲሰሩ
             በማድረግ  ከነገ  ተረኛ  ተረጅነት  ወደ  ነቃ  የኢኮኖሚ  ዘዋሪነት

             የሚያሻግር ፖሊሲ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል፡፡


             179    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   176   177   178   179   180   181   182   183   184   185   186