Page 184 - አብን
P. 184

አብን


             ኢትዮጵያን  በክብር  ያኖረና  የሚያኖር  የኢትዮጵያውያን

             የጀግንነት  ታሪክ  እንደተረት  ተረትና  አልባሌ  ነገር  ተደርጎ
             ሲቀርብ  የነበረው  እኩይ  ምስል  እንዲስተካከል  ይደረጋል፤
             የኢትዮጵያውያን የአገርን ሉዓላዊነት ያስጠበቀና የሚያስጠብቅ
             የተጋድሎ  ባሕል  በክብር  ይዘከራል፡፡  የኢትዮጵያውያን
             የአንድትና  የመተባበር  እንዲሁም  የአገር  ፍቅርና  የድል
             አድራጊነት  ባሕል  የተዘከረባቸው  አውደ  ውጊያዎች  ማለትም
             የጥቁር  ሕዝቦች  የነፃነትና  የአሸናፊነት  ምልክት  የሆነው
             የአድዋ  ድል  በዓል፣  የካራማራ፣  የአምስቱ  ዓመት  የኢትዮ-

             ጣሊያን  ጦርነት  ድል  እና  መሰል  ሕዝባዊ/አገራዊ  ድሎች
             ለትውልድ  ይዘከራሉ፡፡  የአገር  ባለውለታ  ጀግኖችም  በክብር
             ከትውልድ  ትውልድ  ይታወሳሉ፡፡  በሉላዊነት  ሳቢያ  የራሱን
             እንቁ  ባሕል  ንቆ  /ትቶ/  ጎጂ  መጤ  ባሕልን  የሚያንጠለጥል
             ትውልድ  እንዳይፈጠር፤  ይልቁንም  ወጣቱ  አገራዊ  በሆኑ
             ቁሳዊና መንፈሳዊ የማንነቱ አስኳል በሆኑ እሴቶቹና አሻራዎቹ

             ላይ እንዲያተኩር ይሰራል፡፡

             ኢትዮጵያዊ  ውበታችን  በሆኑ  አኩሪ  ባሕሎቻችን፣  የብሔር
             ስብጥር  ልዩነታችን፣  ቋንቋዎቻችን  እንዲሁም  ኃይማኖቶቻችን
             ብዝኃነቶች        ሰበብ      በማድረግ        ኢትዮጵያንና         ሕዝቦቿን
             ለመከፋፈል  የሚደረገውን  ሕግና  መዋቅር  ወለድ  መንግስት-
             አገዝ  ሽብርና  ማኅበራዊ  ሁከት  በማውገዝ  የኢትዮጵያዊነት
             ብሔራዊ ስሜታችንን የሚያበለጽግ ኅብረብሔራዊ ፀጋዎቻችንን

             እናጎለብታለን፤            የኢትዮጵያን         ባለብዙ      ቀለም      አንድ
             አገርነትንም እናጸናለን፡፡



             182    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   179   180   181   182   183   184   185   186   187   188   189