Page 189 - አብን
P. 189

አብን


                  የኪነ-ጥበብ  ሥራ  ከመንግስት  ቁጥጥርና  ሳንሱር  ነጻ

                    ይሆናል።
                  የኪነ-ጥበብ  ሥራዎች  የኢትዮጵያን  የረጅም  ዘመናት
                    ታሪክና  ታላቅነት  እንዲሁም  የኢትዮጵያን  ሕዝብ
                    አንድነትና  በሰላምና  በፍቅር  አብሮ  የመኖር  ልምድ
                    ለማጠናከር እንዲያግዙ ይበረታታሉ።
                  ብሔራዊ  የአገር ውርስና  ቅርስ ለመጠበቅ  የሚያስችሉ
                    ተቋማት        ይቋቋማሉ፤         በስራቸውም          በሥነ-ቅርስ
                    ክብካቤና  በሳይንሳዊ  ጥናት  የተደግፉ  ጥናቶችን

                    የሚያካሄዱ ዘርፎች ይኖሯቸዋል።
                  ለዘመናዊ የኪነጥበብ ሥራዎች ውጤት ማሳያ ዘመናዊ
                    ሙዝየሞች ይቋቋማሉ።
                  የአገሪቱን         የፈጠራና         የኪነ-ጥበብ         ሥራዎችን
                    የሚያነቃቃ ብሔራዊ የኪነ-ጥበብ አካዳሚ ይቋቋማል።
                  የአገሪቱን  የፎክሎርና  ሥነ-ቃላዊ  ሥራዎችን፣  አገር

                    በቀል  ጥበባትንና  እውቀትን  የሚሰበስቡ፣  የሚያጠኑና
                    የሚሰንዱ        እንዲሁም         ለልዩ     ልዩ      መንግስታዊ
                    ፖሊሲዎች  ግብዓት  ሊውሉ  የሚችሉበትን  ሁኔታ
                    የሚያጠኑ ተቋማት በየባሕል አካባቢው ይቋቋማሉ።
                  የኪነ-ጥበብና አገር-በቀል ጥበባት ሥራዎች ትእይንቶች
                    (ኤግዚቢቶች)  ማሳያ  አዳራሾችና  ማእከላት  በየባሕል
                    አካባቢው ይቋቋማሉ።

               3.10.  ማኅበራዊ ካፒታል
                  ለአንድ  አገር  ዘላቂ  ኅልውና  ኣስፈላጊ  ከሆኑ  ጉዳዮች
                    መካከል  ማኅበራዊ  ኃብት  ኣንዱ  ነው፤  ይህንን  ኃብት
                    መንከባከብ የዜጎችና መንግስት ግዴታ ነው።


             187    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   184   185   186   187   188   189   190   191   192   193   194