Page 191 - አብን
P. 191

አብን


                  ጠንካራ  የሥራ  ባሕልና  ሥነ-ምግባር  (work  ethic)

                    እንዲኖርና እንዲስፋፋ አስፈላጊው ጥረት ይደረጋል።
                  በሕብረተሰቡ  አባላት  መካከል  ማኅበራዊ  ትሥሥርና
                    እምነት  እንዲስፋፋ  ለማድረግ  የሚያስችሉ  የማኅበራዊ
                    ካፒታል ትምህርትና ምርምር ተቋማት ይቋቋማሉ።



               3.11.  መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (መያዶች)

                  መንግስታዊ  ያልሆኑ  ድርጅቶች  ለኢትዮጵያ  ሰላምና
                    ልማት  ከፍተኛ  ሚና  ይጫወታሉ።  በመሆኑም  የአገር
                    ውስጥም  ሆነ  ዓለምአቀፍ  መያዶች  በሕብረተሰቡ
                    ልማት ሥራ ጉልህ ሚና እንዲጫወቱ ይበረታታሉ።

                  ለመያዶች  ማነቆ የሆኑ  ሕጎች  ይሻራሉ፤ ለሥራ  ምቹ
                    ሁኔታ ይፈጠርላቸዋል።
                  መያዶች  ገቢያቸውና  የተሰማሩበት  የሥራ  መስክ
                    እየታየ የሚደጎሙበት መንገድ ይመቻችላቸዋል።
                  አገር      በቀል      መያዶች       እንዲስፋፉና         እንዲያድጉ
                    ይበረታታሉ።

                  መያዶች  እንዲበረታቱና  እንዲጠናከሩ  ይደረጋል፤
                    የአገሪቱን  ሕግ  አክብረውና  ከመንግስት  ተጽዕኖና
                    ጣልቃ-ገብነት ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ይደረጋል።
                  በሌሎች  አገሮች  በሰብዓዊ  መብት፣  በልማትና  በሰላም
                    ተጨባጭ  ውጤት  ያስገኙና  ለአገር  ልማትና  እድገት
                    እንደሚበጁ         የሚታመኑ          ዓለምአቀፍ        ግብረሰናይ
                    ድርጅቶች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ይበረታታሉ።



             189    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   186   187   188   189   190   191   192   193   194   195   196