Page 192 - አብን
P. 192

አብን


                  በልዩ ልዩ ተጽእኖዎች ምክንያት የተዘጉ አገር በቀልና

                    ዓለምአቀፋዊ  መያዶች  እንዲከፈቱ  ይደረጋል፤  ሌሎች
                    አዳዲስ መያዶችም እንዲመሰረቱ እናበረታታለን።
                  በተለይ  በዴሞክራሲና  ሰብዓዊ  መብት  እንዲሁም
                    በግብርና፣  በጤናና  ትምህርት  ልማት  ዘርፍ  ለሚሰሩ
                    መያዶች ልዩ ድጋፍ ይደረግላቸዋል።



               3.12.  መገናኛ ብዙኃን

                  የፓርቲያችን  የፓለቲካ  ፍልስፍና  ከሆኑት  ጉዳዮች
                    አንዱ  ብዝኃነት  ሲሆን፣  ብዝኃነት  ከሚገለጽባቸው
                    አንዱ  የመገናኛ-ብዙኃን  (ሚዲያ  ብዝኃነት)  ነው።

                    በመሆኑም  የብዙኃን  መገናኛዎች  የአገሪቱን  ብሔራዊ
                    አንድነትና  የጋራ  እሴቶች  ለማጠናከር  ይሰራሉ፤
                    ባሕላዊና ኃይማኖታዊ እኩልነትንና ሰላማዊ አብሮነትን
                    አክብረው፣  ሙያዊ  ስነ-ምግባርን  ተላብሰው  እንዲሰሩ
                    ይበረታታሉ።
                  የብዙኃን መገናኛዎች ከመንግስት ተጽእኖና ወገናዊነት

                    ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ይደረጋል።
                  የፕሬስ ነጻነት የተረጋገጠ ነው።
                  ሚዲያው ብዝኃነትን ባሕል እንዲያደርግ ይደረጋል።
                  የመንግስትና የግል ፕሬስና ሚዲያ የኢትዮጵያን ሕዝብ
                    ከዳር እስከዳር እንዲደርስ ይደረጋል።
                  የግል  ፕሬስ፣  የግል  ሬዲዮና  ቴሌቪዥን  ጣቢያዎች
                    እንዲከፈቱ ይበረታታል።



             190    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   187   188   189   190   191   192   193   194   195   196   197