Page 204 - አብን
P. 204

አብን


             ከአገር  ውስጥ  ሰላም  እጦት  በተጨማሪ  የኢኮኖሚ  መዳከም፣

             ድህነትና  የዴሞክራሲ  መቀጨጭ  አገሪቱን  የደኅንነት  ስጋት
             ተጋላጭ ያደርጋል፡፡ ታሪካችን እንደሚያረጋግጠው የኢትዮጵያ
             የውስጥ        ተጋላጭነት          በአገሪቱ       ግዛታዊ        አንድነትና
             በጸጥታ/በደኅንነት  ላይ  አሉታዊ  ተጽዕኖ  ካሳደሩ  ምክንያቶች
             አንዱና  ዋነኛው  ነው፡፡  ውስጣዊ  የደኅንነት  ችግሮቻችን
             ከኢትዮጵያ ጋር የተፈጥሮ ኃብትና የድንበር ውዝግብ ላላቸው
             ክልላዊ  የፖለቲካ  ኃይሎችና  ወኪሎቻቸው  ጣልቃ  ገብነት
             እድል በመስጠት  የአገሪቱን ሰላም እንዳይረጋጋ ለማድረግ በር

             ይከፍትላቸዋል፡፡

             በመሆኑም  የአብን  የውጪ  ግንኙነት  ፖሊሲ  የሕዝቦችን
             የውስጥ ሰላምና  ደኅንነት በዘላቂነት ለመጠበቅ ትልቅ ትኩረት
             ሰጥቶ  ይሰራል፡፡  የሰላምና           ደኅንነት  ፖለሲና  ስትራቴጂያችን
             ከላይ  የተዘረዘሩትን  የውስጥ  ተጋላጭነቶች  በመቀነስና

             የአገሪቱና  የሕዝቡን  ፍላጎት  ማስጠበቅ  የሚያስችል  የውጭ
             ግንኙነት  (የፖለቲካ፣  የኢኮኖሚ፣  የወታደራዊ  ዲፕሎማሲ
             ወይም  ዲተረንስ)  የመደራደር  አቅም  የማጎልበቱን  ሂደት
             ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል፡፡











             202    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   199   200   201   202   203   204   205   206   207   208   209