Page 117 - አብን
P. 117

አብን




             በአሁኑ  ወቅት  እየተጀመሩ  ያሉ  የግብርና  ማቀነባበሪያ
             ኢንዱስትሪዎች  ታሳቢ  ያደረገ  ጥሬ  እቃ  በመጠንና  በጥራት
             ማቅረብ  ቁልፍ  ተግባር  ነው፡፡  ኢንዱስትሪዎችን  ሊመግቡ
             የሚችሉ የምርት አቅም ያላቸውን አካባቢዎች በመለየት አርሶ
             አደሮች  ከፋብሪካዎች  ጋር  ትስስር  እንዲፈጥሩ  በማድረግ
             ጥራት  ያለው  ምርት  በማቅረብ  በዋጋ  ተጠቃሚ  እንዲሆኑና
             ፋብሪካዎች  ተወዳዳሪ  እንዲሆኑ  የሁለትዮሽ  ተጠቃሚነት
             ሥርዓት ይዘረጋል፡፡


             አገራችን  በከፍተኛ  መጠን  እና  ደረጃ  በመስኖ  ውኃ  ሊለማ
             የሚችል  መሬት  እንዲሁም  ለዚሁ  ተግባር  የሚሆን    የውኃ
             አቅም ስላላት ትላልቅ መስኖዎች በመገንባት የመስኖ ግብርና
             እንዲስፋፋ ይደረጋል፡፡ይህም ከመኸር ምርት በተጨማሪ አርሶ
             አደሩ  በበጋ  ሁለት  ጊዜ  እንዲያመርት  ያስችላል፡፡  ለመስኖ

             ልማቱ  በዓለምአቀፍ  ገበያ  ሊቀርቡ  የሚችሉ  የአትክልት  እና
             ፍራፍሬ  ዝርያዎችን  በማቅረብ  ጥራት  ያለው  እና  ተወዳዳሪ
             ምርት  በማምረት  እና  በማቀነባበር  ለገበያ  እንዲቀርብ
             የሚያስችል  ስርዓት  ይዘረጋል፡፡  በዘርፉ  የግል  ባለሀብቱ
             እንዲሰማራ  አሁን  ያለውን  ረጅም  ቢሮክራሲ  በማስወገድ
             ባላሀብቱ  በቀላሉ  ብድር፣  መሬት  እና  የባንክ  ሌተር  ኦፈ
             ክሬዲት እንዲያገኝ ስርዓት ይዘረጋል፡፡


             በቆላማው አካባቢ የሚገኙ የእርሻ መሬቶችን ያሉበትን ሁኔታ
             በማጥናት መሬቱን ወስደው ወደ ምርት የገቡትን ባለሀብቶች
             ድጋፍ ማድረግ፤ መሬቱን ወስደው ወደ ሥራ  ያልገቡም ሆነ


             115    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   112   113   114   115   116   117   118   119   120   121   122