Page 160 - አብን
P. 160

አብን


                  የኃይል ቁጠባ ማስገንዘቢያ ተቋም

             ኃይል ከመነጨ በኋላ ከማስተላለፍ ቀጥሎ ኃይል የሚባክነው
             በተጠቃሚዎች  የአጠቃቀም  ጉድለት  ነው።  ይህን  የኃይል
             ብክነት  ለማስቀረት  ከማምረት  ጋር  በተጓዳኝነት  እኩል
             መስራት  ይገባል።  ኃይልን  አለማባከን  ለአገር  ትልቅ  ውለታ
             እንደመዋል  እንዲቆጠር  ማድረግ  የሚያስችል  ከልዮ  ልዩ
             ባለድርሻ አካላት፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና ተቋማትን ያቀናጀ በበጎ
             ፈቃደኝነት  የሚሰራ  ተቋም  መመስራት  ያስፈልጋል።  የኃይል
             ቁጠባ  ግንዛቤን  ለሕዝቡ  በቀላሉ  ተደራሽ  ለማደረግ  የሚዲያ

             ተቋማትን  ይጠቀማል።  ይህንን  ተቋም  በበላይነትም  የኃይል
             ስርጭት ዘርፉ ይመራዋል።

                2.6.3  የተፈጥሮ ጋዝና ማዕድናት
             በየአካባቢው መኖራቸው የተረጋገጠና ጥቅም ላይ እየዋሉ ያሉ
             ማዕድናት የየአካባቢዎችን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ባደረገ መንገድ

             ጥቅም ላይ እንዲውሉ ይደረጋሉ፡፡ ለአገር በቀልና ዓለምአቀፍ
             የማዕድን  ፈላጊና  አልሚ  ተቋማትም  ልዩ  ማበረታቻና  ድጋፍ
             ይደረጋል፡፡  የአካባቢ  ብክለትን  በማያስከትል  መልኩ  የነዳጅና
             ተፈጥሮ  ጋዝ  ፍለጋና  ቁፋሮ  ልማት  ሥራዎችም  ትኩረት
             ይሰጥባቸዋል፡፡















             158    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   155   156   157   158   159   160   161   162   163   164   165