Page 211 - አብን
P. 211
አብን
በኤርትራ ድንበር በኩል የተጀመረው የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ
በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ዘርፍ ጎልብቶ በድንበር አካባቢ ሲከሰቱ
የነበሩ የጸጥታ መስተጓጎሎች ለማስቀረት ይሰራል፡፡ አመርቂ
ፖለቲካዊ ጥምረቶችን እውን በማድረግ ኤርትራ ለኢትዮጵያ
የውጭ ንግድ የተሻለች አማራጭ እንድትሆን የማዘጋጀቱ
ሥራ ቀዳሚ ትኩረት ተሰጥቶት የኢኮኖሚው ትስስር የሰላም
መንገዶችን እንዲያለሰልስ ይደረጋል፡፡
የድንበር ንግድ፣ ሰላምና በውጭ ትብበር ወንጀሎችን መቀነስ
በአንዳንድ አካባቢዎች ማለትም በመተማ፣ ኩርሙክ፣ ሞያሌ
ወዘተ የሚደረጉ የድንበር ዘለል ሕገ-ወጥ ንግዶች ለጸጥታ
መደፍረስና ለተለያዩ ወንጀሎች ምክንያቶች ናቸው፡፡
በመሆኑም የእነዚህንና የመሰል አካባቢዎች የንግድ እንቅስቀሴ
በሕጋዊ ማዕቀፍ ውስጥ በማስገባት የአካባቢዎች የንግድ
መስተጋብር ከወንጀልና ግጭት የጸዳ እንዲሆን ይሰራል፡፡
የአብን ፖሊሲ በጋራ ትብብር የድንበር ግጭቶችና ድንበር
ዘለል ወንጀሎችን ለማስቀረት ያለመ ነው፡፡ አብን ኢትዮጵያ
ከጎረቤት አገራት ጋር ያለባትን የድንበር ውዝግብ በዓለምአቀፍ
ሕጎች መሰረት እንዲፈታ ድርድሮችን በማስጀመር እያገረሹ
በሚነሱ ግጭቶች የሚጠፋውን የሰው ሕይወት ማስቀረትን
ታሳቢ ያደረግ ፖሊሲ ይከተላል፡፡ በተጨማሪም ድንበር ዘለል
የወንጀል ድርጊቶችን በተመለከተ ከጎረቤት አገራት ጋር
የሚደረጉ የወንጀል መከላከል የትብብር ውሎች፤ ከኢንተርፖል
209 ጊዜው አሁን ነው! አብንን ይምረጡ !