Page 228 - አብን
P. 228

አብን


             የአገራችን  አካባቢዎች  በተለይም  በሰሜን  ምዕራብ፣  በሰሜን፣

             በሰሜን  ምስራቅ፣  በምስራቅ፣  በደቡብ  ምስራቅ፣  በደቡብና
             በማዕከላዊ  ኢትዮጰያ  የደረቅ  ወደብ  ተቋማትን  በመገንባት
             የሱዳንን  ወደብ  (Port  Sudan)፣  የኤርትራን  ወደብ  (አሰብን-
             Asab)፣  የጂቡቲን  ወደብ  (Djibouti  port)፣የከፊል  ራስ  ገዝ
             ሶማሊላንድን  ወደብ  (Berbera)  እና  የኬንያን  ወደብ
             (Mombassa)  ለደረቅ  ወደቦቹ  እንደሚኖራቸው  ቀረቤታና
             አመችነት አማራጭን የማስፋት ሥራ መተግበር ያስፈልጋል፡፡


                  የረጅም ጊዜ የፖሊሲ አቅጣጫ

             በረጅም  ጊዜ  ስትራቴጂካዊ  የወደብ  አገልግሎት  በጋራ  ገበያ፣
             በጋራ ኢኮኖሚና ዘርፈ ብዙ ክልላዊ ትብብሮች ማዕቀፍ ውስጥ
             የሚስተናገድበት  አግባብ  እንዲኖር  አብን  ይሰራል  (ከታች
             በሰፊው  ተብራርቷል)፡፡  በአፍሪካ  ቀንድ  የጋራ  የጉሙሩክ

             ሥርዓት፣  የጋራ  ገበያና  የጋራ  ኢኮኖሚ    (custom  union,
             common  marke  and  common  economy)  ሂደታቸውን
             ጠብቀው  እውን  የሚያደርግ  አገራዊ  የፖለቲካ-ኢኮኖሚ
             መርሆችን  በመዘርጋትና  ክልላዊ  ዲፕሎማሲን  በማሳደግ
             ከጂኦፓለቲካዊ  ተጋላጭነትን  የመነጨውን  ጫና  ማቅለል
             ይቻላል፡፡  ከዚህ    ጎን  ለጎን  ክልላዊ  ኃይልንና  ተጠቃሚነትን
             የሚያሳደግ  የኮንፌደሬሽን  ፖለቲካዊ  ጥምረት  ከኤርትራ፣
             ሱዳን፣  ሶማሊያና  ጂቡቲ  ጋር  እውን  እንዲሆን  ጥረት

             ይደረጋል፡፡





             226    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   223   224   225   226   227   228   229   230   231   232   233