Page 231 - አብን
P. 231

አብን


             ከምርጫ  በኋላ  የትኛውም  ወቅቱ  በሚጠይቀው  የትብብር

             መስክ  ከሌሎች  ኃይሎች  ጋር  በመሆን  ከላይ  ከተዘረዘሩ
             ከዲያስፖራ  ባለሃብቶች  ጋር  የተያያዙ  ተግባራትን  በማካናወን
             የአገሪቱን እድገት ለማፋጠን ይሰራል፡፡

             4.4.2 የዲያስፖራ ምሁራን

             ከ1983  ዓ.ም.  ወዲህም  ሆነ  ከዚያ  በፊት  በፖለቲካው
             ጎራባጭነት  የተነሳ  ወይም  የተሻለ  ሥራና  ክፍያ  ፍለጋ  በሽህ

             የሚቆጠሩ  ምሁራን  ወደ  ውጭ  አገር  በመሄድ  እዚያው
             እንደሚኖሩ ይታወቃል፡፡ ተራማጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ምሁራን
             በዝቅተኛ  ደረጃ  ባሉ  የመንግስት  ቢሮ  ክራሲዎች  ውስጥ
             ከመቀጠር  ያለፈ  እድል  እንደማይኖረቸው  የሚያስረዱ  ብዙ
             የሰነድ  ማስረጃዎች  አሉ፡፡  ከእነዚህ  ምሁራን  የአገሪቱን
             መለወጥ  የሚደግፉ  እና  የቻሉትን  እንደሚያደርጉ  የሚታወቅ

             ነው፡፡  የምሁራኑ  ሚና  የትየለሌ  ሲሆን  ከነዚህም  የአገሪቱን
             ፖሊሲዎች  እና  ስትራቴጂዎች  ተችቶ  የማጠናከር፣  ሙያን
             የማካፈልና  የልምድ  ልውውጥ  ማድረግ፣  እንደ  ዲፕሎማት
             ማገልገል  የመሳሰሉትን  መጥቀስ  ይቻላል፡፡  በተጨማሪ
             ምሁራኖቹ  ሊወጡ  የሚገባቸውን  ዘርፈ  ብዙ  ሚና  እንዲወጡ
             የውጭ  ጉዳይ/ሚኒስቴር/  ክፍል  በመቀስቀስ  መርኅ  ተግባር
             በማዘጋጀትና ግንኙነት በመፍጠር ተነሳሽነቱን ይወስዳል፡፡


             4.4.3  በውጭ  አገር  ተወልደው  እዚያው  የሚኖሩ  ትውልደ
             ኢትዮጵያውያን



             229    ጊዜው አሁን ነው!                        አብንን ይምረጡ !
   226   227   228   229   230   231   232   233   234   235   236